ወ/ሮ አዜብ መስፍን እስካሁን ቤተመንግስቱን ለአቶ ኃለማርያም አላስረከቡም መስከረም ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሳት ዘጋቢ እንደገለጠው ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቤተ መንግስቱን ለቀው ባለመውጣታቸው አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ቦሌ ከሚገኘው ቤታቸው ጠዋት እና ማታ ሲገቡና ሲወጡ መንገድ እየተዘጋ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ እየተፈጠረ ከመሆኑም በላይ ከአሁኑ የአካባቢውን ነዋሪዎች እያስመረሩ ነው፡፡ በርግጥ ሥራቸውን ጠ/ሚኒስትር ቢሮ እየገቡ በመስራት ላይ መሆናቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ወ/ሮ አዜብ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል እንደሚገኙ ቢገለጽም ጉዳዩን ከነጻ ወገን ለማጣራት ያደረግነውጥረት አልተሳካም፡፡ የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ለፕሬዚዳንትነት ተመርጠው ቃለመሃላ ከፈጸሙ በኃላ ወዲያውኑ የተወሰዱት ወደ ቤተመንግስት እንደነበር በእርሳቸው የህይወት ታሪክ ላይ የተጻፈው ”ዳንዲ የነጋሶ መንገድ ” የሚለው መጽሀፍ ያመለክታል። አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ግን እስካሁን ድረስ ምንነቱ ባልታወቀ ምክንያት ወደ ቤተመንግስቱ አልገቡም:: በቤተመንግስቱ ቅጥር ግቢ ከ100 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ባለው ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ውስጥ ለመግባት አቶ መለስና ቤተሰባቸው ባይታደሉም ህንጻው እየተጠናቀቀ በመሆኑ አቶ ኃለማርያምና ቤተሰቦቻቸው በቅርቡ ይረከቡታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የአቶ ሀይለማርያምን ሹመት ያልተቀበሉት በርካታ የኦህዴድ ከፍተኛ የአመራር አባላት የማእከላዊ ስብሰባቸውን በአዳማ ከተማ እያካሄዱ ነው። የስብሰባውን ሂደት በተመለከተ መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን። Recommend on Facebook Tweet about it Subscribe to the comments on this post Print for later Bookmark in Browser Tell a friend ‹ Previous Next › Related posts የቀድመዋ እመቤት ጋሻ አነሱ! Ethiopia’s homeless Prime Minister Ethiopian Airlines in trouble under an incompetent CEO Ethiopia: Azeb Mesfin leaves Palace Leave a Comment Click here to cancel reply. Name* Email* Website Submit Comment